ዋና ጎራዎች


ድርጅትዎን በነጻ ያስተዋውቁ!

ወደ ኢዜጋ ድረ ገጽ እንኻን በደህና መጡ! ይህ የድርጅቶች ማዉጫ የተዘጋጀው በኢትዮጵያ ዉስጥ ያሉ ሁሉ ካምፓኒዎች ኢንዲመዘገቡ እና ስራቸውን እንዲያስተዋውቁ ነው፣ ማንኛውም ሰው ወይንም ካምፓኒ እዚህ ድረ ገጽ በነጻ መመዝገብ ይችላል፣ የድርጅቱ ዝርዝርም ማስገባት ይችላል፣ ክድርጅቶች ማውጫው ሌላ፣ ኢዘጋ የተለያዩ ገጾች አሉት - ዜና፣ መዝናኛ፣ ስራ፣ ሪል እስቴት፣ ማስተዋቅያ፣ የመሳሰሉት ድረ ገጾች አሉት ለበለጠ መረጃ ኢሜል በዚሁ አድራሻ ይላኩልን፡ contact@ezega.com, ወይንም በዚህ ስልክ ይደውሉልን፡ 0912-706091 እናመሰግናለን!


የኢትዮጵያ ምርት ገበያ

Lideta, Addis Ababa
+251 11 554 7001
ፋክስ +251 11 554 7010
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በሃገራችን አዲስ ውጥን ሲሆን በአፍሪካም በአይነቱ የመጀመሪያው ነው፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ራዕይ ዋላ ቀር እርሻ ላይ የተመሰረተውን የሃገሪቱ ግብርና ላይ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት ከገበሬው እስከ ነጋዴው፣ ከነጋዴው እስከ አቀናባሪው፣ ከአቀናባሪው እስከ ላኪው ሁሉንም ተገበያዮች የሚያገለግል አዲስ የግብይት ስርዓት መፍጠር ነው፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የገበያ አስተማማኝነትን፣ ደህንነትንና ቅልጥፍናን በማምጣት የወደፊቷን ኢትዮጵያ የሚያሳይ ገበያ ነው፡፡ ገበያው በምርቱ ዘርፍና በኢንዱስትሪው ማለትም በትራንስፖርት፣ በአቅርቦት፣ በባንክና በፋይናንስ አገልግሎት ዘርፎችና ሌሎች መካከል ተመጣጣኝ የሆነ እድገት የሚኖርበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የሁሉም ምርት ተገበያዮች ምርት በማከማቸት፣ የጥራት ደረጃ በማውጣት፣ በማሻሻጥ፣ ከስጋት ነጻ የሆነ ክፍያና ርክክብ በመፈጸም የሚፈልጉትን አስተማማኝ የሆነ ጥበቃ ያደርጋል፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ለሁሉም ተገበያዮች ወቅታዊ የገበያ መረጃ በመስጠት ተዓማኝነትና ግልጽነትን ይፈጥራል:: ይህንም የሚያደርገው ለግብይት፣ ምርት ለማከማቸት፣ ለክፍያና ርክክብ እንዲሁም ለቢዝነስ ግንኙነትና ለውስጣዊ ግንኙነቶች በግልጽ የሚታዩ ህጎችን በማስቀመጥ ነው፡፡ የምርት ገበያው የገበያ አስተማማኝነትን የሚፈጥረው በ3 ዋና ዋና ደረጃዎች ሲሆን እነሱም በምርቱ፣ በክፍያ እና በተገበያዮች ነው፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ግብይት የጀመረው ሚያዚያ 2001 ዓ.ም. ሲሆን ስራውን ሲጀምርም ለግብረናውና ለንግዱ ኢንዱስትሪም የአባልነት ግብዣ አቅርቧል፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በዘመናዊ ግብይቱ ተጠቃሚ የሚደርገው ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት ስትገበያይባቸው በቆየችባቸው ምርቶች ነው፡፡ ኢትዮጵያ ባህላዊ ከሆነው የግብይት ስርዓት ወደ ዘመናዊ የግብይት ስርዓት ለመለወጥ ትፈልጋለች፡፡ ይህ ደግሞ በግብይትና ምርት ሂደቶች ላይ ያተኩራል፡፡ ምርት ገበያው ከመቋቋሙ በፊት በኢትዮጵያ የነበረው የእርሻ ውጤቶች ግብይት ከፍተኛ ዋጋ የሚጠይቅና ስጋት የተሞላበት ነበር፡፡ መጭበርበርን በመፍራት ከጠቅላላው ምርት አንድ ሦስተኛው ብቻ ለግብይት በሚቀርብበት ሀገር ሻጮችና ገዥዎች የሚገበያዩት የሚያውቁትን እያፈላለጉ ነው የሚገበያዩት፡፡ ግብይት የሚካሄደው ምርቱን በዓይን በመመልከት ብቻ ነበር፡፡ ለምርት ጥራትና ብዛት መተማመኛም አልነበረም፡፡ ይህ ደግሞ የገበያ ዋጋን በማናር በተጠቃሚው ላይ የዋጋ ጫና አሳድሯል፡፡ የሃገራችንን ምርት 95 በመቶ የሚያመርቱት አነስተኛ ገበሬዎች ታዲያ በቂ የገበያ መረጃ ስለማይኖራቸው በሚያውቁት የገበያ ቦታ ነጋዴው በቆረጠላቸው ዋጋ ይሸጡ ነበር:: ተደራድሮ በተሸለ ዋጋ መሸጥና የገበያውን ስጋት መቀነስ አይችሉም ነበር፡፡ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አዲስ አሰራር በመዘርጋት ሁሉም ተገበያይ አስተማማኝ የሆነ ግብይት እንዲያካሂድ አስችሏል፡፡ ይህ የገበያ ስርዓት ገዥና ሻጭ በፍጥነት እንዲገናኙና እንዲገበያዩ ያደርጋል፡፡ የሁለቱንም ፍላጎት በመጠበቅ የኢትዮጵያን እርሻ ወደ አዲሱ ሚሊኒየም ማሸጋገሪያውና ግልጽነት፣ ውጤታማነትና በአዳዲስ ፈጠራዎች የተላበሰ ገበያ መፍጠሪያው ጊዜ አሁን ነው፡፡ በዓለም ዓቀፉ ገበያም ቦታ እንዲኖራት ማድረጊያ ጊዜውም አሁን ነው፡፡







በአቅራብያው የሚገኙ ተመሳሳይ ድርጅቶች


አዲሲንያ ሆቴል
አዲሲንያ ሆቴል አዲስ አበባ አሉ ከሚባሉ ምርጥ ሆቴሎች አንዱ ነው፣ በሰርቪስ፣ በጥራቱና በምቾቱ ተወዳዳሪ የሌለው ሆቴል ነው፣ ዛሬ ይምጡና ይጎብኙን! Tel: +251-11 662 3634, +251-11 662 3439, +251-11 869 5408 Email: info@addissiniahotel.com, reservation@addissiniahotel.com
http://www.addissiniahotel .com
የኢትዮጽያ አየር መንገድ
የኢትዮጽያ አየር መንገድ
http://www.ethiopianairlines.com/